Categories
Amharic

ከመቼውም ጊዜ በላይ እንጠንቀቅ

ኮቪድ-19 በአለማችን ከተከሰተ ዕለት አንስቶ እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለከፋ ህመም ፣ ለበርካቶች ደግሞ ህልፈተ ህይወት ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን አስከትሏል፡፡ በሃገራችን አንድ በኮቪድ-19 ቫይረስ የተያዘ ግለሰብ ከተመዘገበበት ዕለት መጋቢት 4/2012 ጀምሮ 230‚944 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ፣171,980 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፤983 ሰዎች በፅኑ ህሙማን ክፍል ይገኛሉ። እንዲሁም 3‚208 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

ባሳለፍነው 7 ቀናት (መጋቢት28- ሚያዝያ 04/2013) 183 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡በዚሁ ሳምንት አዲስ አበባን ጨምሮ ከፍተኛ የሞት ቁጥር ያስመዘገቡ ክልሎችን ስንመለከት:-

*አዲስ አበባ 98

*ኦሮሚያ 30

*አማራ 14

*ሐረሪ 14

*ሲዳማ 10 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ 

ሁሉም የማሕበረሰብ ክፍል የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ መጠቀም ፣ የእጅን ንጽህና በተደጋጋሚ በመጠበቅ እና በማንኛውም ቦታ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ አዘውትረን የኮቪድ-19 የመከላከያ መንገዶችን እንድንተገብር የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሳስባል፡፡

#እንድናገለግልዎማስክዎንያድርጉ

#COVID19Ethiopia

#Directive30

#COVID19VACCINE

#NOMASKNOSERIVCE  

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *