Categories
Amharic

የኮሮና ቫይረስ (የኮቪድ-19) በሽታ ምላሽ አሰጣጥን አስመልክቶ የተዘጋጀ መግለጫ ግንቦት-13

መደበኛ የ24 ስዓት ዕለታዊ መግለጫ ከተሰጠ በኋላ በደረሰን አዲስ መረጃ መሰረት በሀረሪ ክልል፤  በተደረገ 12 የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ አንድ (1) ሰው የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥም አስር (10) ሰዎች በምርመራ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ሶስት መቶ ዘጠና ዘጠኝ (399) ደርሷል፡፡ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘበት ግለሰብ የ37 ዓመት የሀረር ከተማ ነዋሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሲሆን የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌለው ነው፡፡

በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ  የሁኔታ መግለጫ

አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ69,519
በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ3759
በዛሬው ዕለት በበሸታ መያዛቸው በላብራቶሪ የተረጋገጠ10
በአጠቃላይ በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ከህክምና ውስጥ ያሉ269
በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ0
አዲስ ያገገሙ1
በአጠቃላይ ያገገሙ123
በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ5
ወደ ሀገራቸው የተመለሱ2
እስከ አሁን ድረስ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር399

የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ  ሥርጭት መጨመርን ከግንዛቤ በማስገባት ሕብረተሰቡ ጥንቃቄዎችን አዘውትሮ እንዲተገብር ያሳስባሉ። በበሽታው መያዛችን ዕለት-ተዕለት በምናደርገው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የሚወሰን መሆኑን በማስታወስ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ አራቱን የ’’መ’’ ህጎች ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት እንድንከላከል በጥብቅ እናሳስባለን።  

  • መራራቅ፡ አካላዊ ርቀት መጠበቅ፣
  • መታጠብ፡ እጅን በተደጋጋሚ በውሃና በሳሙና መታጠብ፣
  • መቆየት፡ አስገድጅ ካልሆነ ቤት ውስጥ መቆየት እንዲሁም
  • መሸፈን፡ ከቤታችን ወጥተን ስንቀሳቀስ የአፍንና የአፍንጫ መሸፈኛ (የፊት ማስክ) መጠቀም

በማንኛውም ሰዓት ጥቆማ ለመስጠትና መረጃ ለማግኘት እንዲሁም በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው ግለሰቦች ሪፖርት ለማድረግ በነፃ የስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 ወይም በመደበኛ የስልክ ቁጥር 0118276796 በመደወል ወይም በኢሜል አድራሻችን ephieoc@gmail.com በመጠቀም ወይም ባሉበት ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት በስልክ እንዲያሳውቁ እንጠይቀለን፡፡

ዶ/ር ሊያ ታደሰ

የጤና ሚኒስትር

ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓ.ም

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *