Categories
English

Status update on COVID19 Ethiopia May 1, 2021

Categories
Amharic

የፋሲካ እና የስቅለት በዓልን በማስመልከት የጤና ሚኒስቴር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ መልእክት አስተላለፉ።

የኮቪድ-19 ቫይረስ አሁንም አሳሳቢ መሆኑን እንደቀጠለ በሀገራችንም የላብራቶሪ ምርመራ ከሚደረግላቸው ሰዎች አኳያ በየቀኑ ከአንድ ሺ በላይ ሰዎች በቫይረሱ እንደሚያዙ እና በጽኑ ህክምና ክፍል ገብተው በከፋ ህመም እንደሚሰቃዩ፤በርካቶች ደግሞ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን እያጡ እንዳሉ እና የከፋ ጊዜ ላይ መድረሳችንን ገልፀዋል። አያይዘውም ሕብረተሰቡ የኮቪድ-19 የመከላከያ መንገዶችን ሳይዘናጋ እንዲተገብር እና የሚቆጣጠረውን አካል ሳይጠብቅ መተግበር ይኖርበታልም ብለዋል።

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት መስፈርቱን የሚያሟሉ ዜጎች ሁሉ ክትባቱን ሊወስዱ እንደሚገባ እና ነገር ግን ክትባት የመከላከያ መንገዶችን የሚተካ ስላልሆነ የኮቪድ 19 መከላከያ መንገዶችን ለአፍታም ቢሆን ሳንዘናጋ መተግበር  እንደሚያስፈልግ ሚኒስተሯ አሳስበዋል።

በዚህ ሀይማኖታዊ በአል ላይ በእምነት ተቋማት መሰባሰቦች፤የመገበያያና የትራንስፖርት ቦታዎች ላይ መጨናናቆች ሊኖሩ ስለሚችሉ እየተስፋፋ ለመጣው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መባባስ ምክንያት ላለመሆን የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ እንጠቀም፤ርቀታችንን እና የእጆቻችንን ንጽህና እንጠብቅ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላለፈዋል፤በዓሉም የሰላም የደስታ እና የጤና እንዲሆን መልካም ምኞታቸውንም ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገልፀዋል፡፡

#መልካምበዓል

#እንድናገለግልዎማስክዎንያድርጉ

#COVID19Ethiopia #NOMASKNOSERIVCE  

Categories
Amharic

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሁሉንም ሀገራት ያዳረሰ፤ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል የሚያጠቃ፤ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውስ እንዲሁም ለሞት የዳረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የስቅለት በዓልን ስናከብር ለስግደት ወደ ቤተ ክርስቲያን በምንሄድበት ወቅት የኮቪድ-19 መከላከያ መንገዶችን ማለትም:-

*ርቀትን መጠበቅ

*ማስክ ማድረግ

*የእጅን ንጽህና መጠበቅ

*ጉንፋን መሰል የህመም ስሜቶች እና ምልክቶች የሚያዩ ከሆነ እንዲሁም የኮቪድ-19 ቫይረስ ካለበት ሰዉ ጋር የቅርብ ንክኪ ከነበረዎት እራስዎን በመለየተ ምርመራ ማድረግ እና ፅሎትዎንና ስግደትዎን በቤት ውስጥ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኝ ግለሰብ፤ቤተሰብ፤መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤የሐይማኖት ተቋማት፣ሲቪክ ማህበራት፤አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፤የጤና ባለሙያዎች፤መምህራንና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ማስክ ማድረግ፣የእጃቸውን ንጽህና በተደጋጋሚ መጠበቅና በየትኛውም ቦታ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ ተገቢውን የጥንቃቄ መንገዶችን በመተግበር የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያደርሰውን ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች በጋራ እንድንከላከል የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጥሪውን ያቀርባል፡፡

#መልካምየስቅለትበዓል

#እንድናገለግልዎማስክዎንያድርጉ

#COVID19Ethiopia

#NOMASKNOSERIVCE  

Categories
Amharic

የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ ሚያዚያ 22 2013

Categories
English

Status update on COVID19 Ethiopia April 30, 2021