Categories
Amharic

የኮሮና ቫይረስ (የኮቪድ-19) በሽታ ምላሽ አሰጣጥን አስመልክቶ የተዘጋጀ መግለጫ ሚያዝያ-26

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 1758 የላብራቶሪ ምርመራ አምስት (5) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ  ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር መቶ አርባ (140) ደርሷል፡፡ የላብራቶሪ ምርመራው የተደረገው በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት፣ በብሄራዊ የእንስሳት ጤና በሽታዎች ምርመራ ማዕከል፣ በአርማውር ሃንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት፣ በኢንተርናሽናል ክሊኒካል ላብራቶሪስ፣ በአዳማ የህብረተሰብ ጤና ምርምርና ሪፈራል ላብራቶሪ፣ በአማራ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ በትግራይ ጤና ምርምር ኢንስቲትዩት፣ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ላቦራቶሪ እና በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ላብራቶሪ የተከናወነ ነው፡፡ የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታም እንደሚከተለው ቀርቧል፣

ተ.ቁዜግነትመኖሪያ ቦታእድሜፆታየውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክበበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት
1ኢትዮጲያዊ24ወንድከፑንትላንድ የተመለሰና በጂግጂጋ  አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ 
2ኢትዮጲያዊ23ወንድከፑንትላንድ የተመለሰና በጂግጂጋ  አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ 
3ኢትዮጲያዊ20ወንድከፑንትላንድ የተመለሰና በጂግጂጋ  አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ 
4ኢትዮጲያዊባህር ዳር17ወንድ ያለው
5ስዊድናዊ (ትውልደ ኢትዮጵያዊ )19ወንድከስዊድን የተመለሰና በአዲስ አበባ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ 

በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ  የሁኔታ መግለጫ

አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ24,088
በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ1758
በዛሬው  ዕለት በበሸታ መያዛቸው በላብራቶሪ የተረጋገጠ5
በአጠቃላይ በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ከህክምና ውስጥ ያሉ60
በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ0
አዲስ ያገገሙ0
በአጠቃላይ ያገገሙ75
በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ3
ወደ ሀገራቸው የተመለሱ2
እስከ አሁን ድረስ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር140

የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመከላከል ሕብረተሰቡ ጥንቃቄዎችን  አዘውትሮ ከመተግበር መዘናጋት እንደሌለበት ጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጥብቅ ያሳስባሉ፡፡ ሕብረተሰቡ በአንድ ቦታ መሰባሰብን በማስወገድ፣ እጅን አዘውትሮ በመታጠብ፣ በአካል ንክኪ የሚደረግ ሰላምታን በመተው፣ ሰዎች በሚሰበሰቡበት ቦታዎች ላይ የአፍንና የአፍንጫ መሸፈኛ (የፊት ማስክ) በማድረግና አካላዊ መራራቅን ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት እንዲከላከል እናሳስባለን፡፡

በማንኛውም ሰዓት ጥቆማ ለመስጠትና መረጃ ለማግኘት እንዲሁም በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው ግለሰቦች ሪፖርት ለማድረግ በነፃ የስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 ወይም በመደበኛ የስልክ ቁጥር 0118276796 በመደወል ወይም በኢሜል አድራሻችን ephieoc@gmail.com በመጠቀም ወይም ባሉበት ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት  በስልክ እንዲያሳውቁ እንጠይቀለን፡፡

ዶ/ር ሊያ ታደሰ

የጤና ሚኒስትር

ሚያዝያ 26፣ 2012 ዓ.ም

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *